በሰሜን አፍሪካ እና በመካከለኛው ምሥራቅ ያለው ሕዝባዊ እንቅስቃሴ በኢትዮጵያም ሊከሰት ይችላል ወይ? የሰሜን አፍሪካ ነውጥ ኢትዮጵያ ውስጥ ሊከሰት ይችላል በሚል ተቃዋሚ ፓርቲዎች የሚያራምዱት ነው። የእኛ ሕገ መንግሥት ትግሎች በሰላማዊ መንገድ እንዲካሄዱ ሰፊ ጎዳና የከፈተ ነው። ከዚህ ውጭ የሚደረግ የሥልጣን ለውጥ ሕገ ወጥ መኾኑን አስቀምጧል። እያንዳንዱ ዜጋም ሕገ መንግሥቱን ማክበር እና ማስከበር እንዳለበት አስቀምጧል። በዚህም ላይ ከዐሥር ወር በፊት ምርጫ ተካሂዶ ኅብረተሰቡም የነበረው መንግሥት እንዲቀጥል በካርዱ ብይን ሰጥቷል። ኅብረተሰቡ ከዚያ በፊት የነበረውን ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ ዐይቶ በምርጫው እንቅስቃሴ ላይ ሐሳቡን ገልጧል። በተነጻጻሪ ከእናንተ በተሻለ የልማት ሥራ የሚሠራ የለንም ብሎ የአምስት ዓመት ኮንትራት ለኢሕአዴግ ሰጥቷል። ሕዝቡ ኢሕአዴግን እንዲሠራ ብቻ አይደለም ዕድል የሰ...
|
|||
No comments yet, be the first one to post comment.