እዚህ፣ አሁን እየሆነ ያለው በምንም መልኩ እዚያ አሁንም ሆነ በቅርቡ ሊካሄድ የሚችል አይደለም። እዚህ ሰውየው በሚያራምደው ሐሳብ ምክንያት በወንጀልኝነት አይፈረጅም፤ እዚያ ግን የሞት ፍርድ የተበየነበት ተፈላጊ “ወንጀለኛ” ነው። አድማጮቹና ተወያዮቹም እንዲሁ እዚህ በወንጀል ተባባሪነት የሚከሳቸው የለም፤ እዚያ ግን በአቶ መለስ ፍርድ ቤት በአባሪነት ሊከሰሱ እንደሚችሉ ያውቁታል። ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ፤ ስቶክሆልም መጋቢት 3፣ 2003 ይህ የስዊድን ዋና ከተማ ስቶክሆልም ነው፤ ሰውየው ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ፤ አድማጮቹና ተወያዮቹ ደግሞ እዚህ የሚኖሩ “የግንቦት 7” አባላት፣ ደጋፊዎች እና ሰውየውን ለመስማት የተሰበሰቡ ሌሎችም ኢትዮጵያውያን ናቸው። ያ ደግሞ የእነዚህ ሰዎች ነፍስና ደም የታተመበት አገር ነው- ኢትዮጵያ። ሆኖም እነርሱ እዚህ አሁን ስለሚነጋገሩበት ጉዳይ እዚያ በአደባባይ መነጋገር የሚታሰብ...
|
|||
No comments yet, be the first one to post comment.