published
745 days, 7 hours, 56 minutes ago
posted by
admin
745 days, 8 hours, 4 minutes ago
Wednesday, May 05, 2010 5:29:18 AM
GMT
Wednesday, May 05, 2010 5:21:31 AM
GMT
የ2002 ምርጫ ሊደረግ ከአንድ ወር በታች ቀርቶታል። ገዢው የህወሓት/ኢህአዴግ መንግሥት ”ነጻና ፍትሃዊ ምርጫ እንዲሆን ለማድረግ የነበረኝን ቁርጠኝነት እያሳየሁ ነው” ይላል። የአውሮፓ ሕብረት ታዛቢዎችም ምርጫውን ለመታዘብ አዲስ አበባ ገብተዋል። መድረኩ ባለፉት ሦስት ሣምንታት ብቻ በመቱ፣ በወልቂጤ፣ በደብረ ብርሃን፣ በደሴ፣ በወልዲያ፣ በኮምቦልቻ እንዲሁም በተለያዩ የአዲስ አበባ ወረዳዎች ታላላቅ ህዝባዊ ስብሰባዎችን እያደረገ ነው። በአቶ ኃይሉ ሻውል የሚመራው መኢአድ በአዋሳ፣ በአቶ ልደቱ የሚመራው ኢዴፓ ደግሞ በአለታ ወንዶ፣ ጎንደርና ባህር ዳር ህዝባዊ ስብሰባዎች ያደረገ ሲሆን፤ የምርጫ ዘመቻቸውን አጧጥፈውታል።
|
No comments yet, be the first one to post comment.