የፊታችን ምርጫ ቀልድ ነው፤ መድረኩ ግን መሳተፉ ይበጀዋል

published 745 days, 7 hours, 56 minutes ago posted by adminadmin 745 days, 8 hours, 4 minutes ago
Wednesday, May 05, 2010 5:29:18 AM GMT Wednesday, May 05, 2010 5:21:31 AM GMT
የ2002 ምርጫ ሊደረግ ከአንድ ወር በታች ቀርቶታል። ገዢው የህወሓት/ኢህአዴግ መንግሥት ”ነጻና ፍትሃዊ ምርጫ እንዲሆን ለማድረግ የነበረኝን ቁርጠኝነት እያሳየሁ ነው” ይላል። የአውሮፓ ሕብረት ታዛቢዎችም ምርጫውን ለመታዘብ አዲስ አበባ ገብተዋል። መድረኩ ባለፉት ሦስት ሣምንታት ብቻ በመቱ፣ በወልቂጤ፣ በደብረ ብርሃን፣ በደሴ፣ በወልዲያ፣ በኮምቦልቻ እንዲሁም በተለያዩ የአዲስ አበባ ወረዳዎች ታላላቅ ህዝባዊ ስብሰባዎችን እያደረገ ነው። በአቶ ኃይሉ ሻውል የሚመራው መኢአድ በአዋሳ፣ በአቶ ልደቱ የሚመራው ኢዴፓ ደግሞ በአለታ ወንዶ፣ ጎንደርና ባህር ዳር ህዝባዊ ስብሰባዎች ያደረገ ሲሆን፤ የምርጫ ዘመቻቸውን አጧጥፈውታል።

No comments yet, be the first one to post comment.

To post your comment please login or signup