የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ አንድነት መድረክ በባህር ዳር ከተማ በሚገኘዉ ስቴዲየም በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዉያን ባሉበት ታላቅ ህዝባዊ ስብሰብ ትላንት ጥር 2 ቀን 2002 ማድረጉን ከስፍራዉ የደረሰን ዜና ያመለክታል። የክልሉ የገዢዉ ፓርቲ ባለሥልጣናት ህዝቡ ወደ ስብሰባዉ እንዳይሄድ በጥቅም ላይ የተመሰረቱ ስብሰባዎች በየቀበሌዉና በየትምህርት ቤቶቹ መድረኩ ህዝባዊ ስብሰባ በጠራበት ቀንና ሰዓት አዘጋጅተዉ እንደነበረም የደረሰን ዜና አክሎ ገልጿል።
(more)